የጌዴኦ ልማት ማህር በዲላ ከተማ የአጼ ዳዊት ትምህርት ቤት የማስፋፊያ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 26/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ የጌዴኦ ልማት ማህበር በጥንታዊው አጼ ዳዊት ትምህርት ቤት ቅር ግቢ ውስጥ የማስፋፊያ ግንባታ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የልማት ማህበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብዙነህ ንጉሴ አጼ ዳዊት ትምህርት ቤት በ1945 ዓ.ም እንደተመሠረተና ጥንታዊ መሆኑን በመጥቀስ ካስቆጠረው ዕድሜ አንጻር ብዙ ዕድሳት፣ ልማትና ማስፋፊያ ሳይደረግለት መቆየቱን አስረድተዋል።
የአጼ ዳዊት 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፕሮጀክት ግንባታ ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተጀመረ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። 4 ክፍሎች ያሉትና እያንዳንዱ ክፍል 200 ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑንም አክለዋል።
ግንባታው በ9 ቀናት ውስጥ ከ39 መቶ በላይ መድረሱን ተገልጿል።
ለ2016 ዓ.ም ተማሪዎችን ተቀበሎ የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛልም ተብሏል፡፡
የልማት ማህበሩ ሰብሳቢ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ የከተማው ሕብረተሰብ፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶች እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ለትምህርት ጥራት የሚደረገው ጥረት እንዲረጋገጥ የኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ እስራኤል ብርሃኑ – ከፍስሐገነት ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ