የጌዴኦ ልማት ማህር በዲላ ከተማ የአጼ ዳዊት ትምህርት ቤት የማስፋፊያ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 26/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ የጌዴኦ ልማት ማህበር በጥንታዊው አጼ ዳዊት ትምህርት ቤት ቅር ግቢ ውስጥ የማስፋፊያ ግንባታ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የልማት ማህበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብዙነህ ንጉሴ አጼ ዳዊት ትምህርት ቤት በ1945 ዓ.ም እንደተመሠረተና ጥንታዊ መሆኑን በመጥቀስ ካስቆጠረው ዕድሜ አንጻር ብዙ ዕድሳት፣ ልማትና ማስፋፊያ ሳይደረግለት መቆየቱን አስረድተዋል።
የአጼ ዳዊት 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፕሮጀክት ግንባታ ሐምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተጀመረ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። 4 ክፍሎች ያሉትና እያንዳንዱ ክፍል 200 ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑንም አክለዋል።
ግንባታው በ9 ቀናት ውስጥ ከ39 መቶ በላይ መድረሱን ተገልጿል።
ለ2016 ዓ.ም ተማሪዎችን ተቀበሎ የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛልም ተብሏል፡፡
የልማት ማህበሩ ሰብሳቢ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ የከተማው ሕብረተሰብ፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶች እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ለትምህርት ጥራት የሚደረገው ጥረት እንዲረጋገጥ የኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ እስራኤል ብርሃኑ – ከፍስሐገነት ጣቢያችን

More Stories
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ
ክቡር የሆነውን የሰውን ሕይወት ለመታደግ ደም በመለገስ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የይርጋጨፌ ከተማ ጤና ጽህፈት ቤት አሳሰበ