አርባምንጭ ከተማ ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱ ተረጋገጠ
አርባምንጭ ከተማ በ2018 የውድድር ዘመን ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።
አዞዎቹ ወደ ታችኛው ሊግ መውረዳቸውን ያረጋገጡት በ36ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በፋሲል ከነማ 2ለ0 በመሸናፋቸው ነው።
ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለአፄዎቹ ሁለቱንም የማሸነፊያ ጎሎች ታምራት እያሱ አስቆጥሯል።
ውጤቱን ተከትሎ በ2016 የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ተመልሶ ሲሳተፍ የነበረው አርባምንጭ ከተማ ለሁለት ዓመታት በዋናው የሊግ ዕርከን ሲሳተፍ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት ወደ ከፍተኛ ሊጉ መውረዱ ተረጋግጧል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ዴክላን ራይስ የአርሰናል የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ተመረጠ
ፖርቹጋልን ያስደነገጠው ያልተጠበቀው አቻ ውጤት!
አርጅቶ ያልደከመው ሊዮኔል ሜሲ