አርባምንጭ ከተማ ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱ ተረጋገጠ
አርባምንጭ ከተማ በ2018 የውድድር ዘመን ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።
አዞዎቹ ወደ ታችኛው ሊግ መውረዳቸውን ያረጋገጡት በ36ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በፋሲል ከነማ 2ለ0 በመሸናፋቸው ነው።
ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለአፄዎቹ ሁለቱንም የማሸነፊያ ጎሎች ታምራት እያሱ አስቆጥሯል።
ውጤቱን ተከትሎ በ2016 የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ተመልሶ ሲሳተፍ የነበረው አርባምንጭ ከተማ ለሁለት ዓመታት በዋናው የሊግ ዕርከን ሲሳተፍ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት ወደ ከፍተኛ ሊጉ መውረዱ ተረጋግጧል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሪያል ማድሪድ ያን ዲዮማንዴን በታሪካዊ የዝውውር ክፍያ አስፈረመ
ብሩኖ ጊማሬስ የሕክምና ምርመራውን በስኬት አጠናቀቀ
9 ክለቦች በአዲስ አሰልጣኞች ፍልሚያቸውን የሚጀምሩበት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ