ፖርቹጋልን ያስደነገጠው ያልተጠበቀው አቻ ውጤት!
በእግርኳስ ጨዋታው ዓለም አንዳንድ ጊዜ ክህሎት እና ስም ብቻ ለድል አያበቁም።
ይህ ትናንት ምሽት የታየው የፖርቹጋል እና የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጨዋታ፣ በትክክል ይህንን እውነታ የሚያረጋግጥ ነበር።
ፖርቹጋል ትናንት ሜዳውን የረገጠችው በጨዋታው የአሸናፊነት የክብር ዘውዷን እንደምትቀዳጅ በሚያረጋግጥ “የንጉሣዊ እብሪት” ቢሆንም፣ በሜዳው ላይ የጠበቃቸው ግን የረቀቀ “ታክቲካዊ ጦርነት” ነበር።
በወረቀት ላይ ፖርቹጋል የነበራት ስብስብ እና የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የሚያስፈራ ነበር።
እያንዳንዱ ተጫዋች በአውሮፓውያን ታላላቅ ሊጎች የተፈተነ፣ ታክቲካዊ ዝግጅታቸውም እንደ እሳት የተሰላ ነበር።
ሆኖም፣ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ጨካኝ እና ያልተገራ የድል ጥማት ሲገጥሟቸው፣ ያ ሁሉ “የሚያንቦለቦል ተሰጥኦ” እንደ ጉም በኖ ጠፋ።
የፖርቹጋል ኮከቦች ለኮንጎ ወኔ ምላሽ የሚሰጡበት ታክቲካዊ ቀመር መፈለግ ተስኗቸው፣ ሜዳው ላይ በስሜትም በጨዋታም ኪሳራ ውስጥ ገብተው ታዩ።
ብዙዎች የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ብሔራዊ ቡድን ከፖርቹጋል አንፃር እንደ መሪ ተዋናይ ሳይሆን እንደ ረዳት ተዋናይ ብቻ ነበር የቆጠሯቸው።
ነገር ግን፣ “ሌኦፓርድስ” የተባሉት የኮንጎ ጀግኖች፣ የተጻፈላቸውን የሽንፈት ታሪክ ቀደዱት።
ኮንጎ በምሽቱ ያሳየችው ኳስ ብቻ ሳይሆን፣ የማይበገረውን የሰው ልጅ መንፈስ ነበር።
ፖርቹጋልን በታክቲክ በማጠር፣ የኳስ ቁጥጥሯን ወደ ምንምነት ቀየሩት።
የመጨረሻው ደቂቃ እስኪደርስ ድረስ በነበራቸው የሰውነት ጥንካሬ እና የድል ፍላጎት፣ የፖርቹጋልን ደጋፊዎች ጭምር በዝምታ አስዋጡ።
ይህ ጨዋታ ለዘመናዊ እግር ኳስ ትልቅ ትምህርት ነው። ስም እና ታሪክ ሜዳ ላይ አይገቡም።
ወደ ሜዳ መግባት የሚገባው 90 ደቂቃ ሙሉ ለሚታገሉት፣ ለሚራቡት እና ለሚደክሙት ብቻ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አሳዩ።
ይህ ጨዋታ ለረጅም ጊዜ ሲወሳ የሚኖር እና ለታዳጊ ሀገራት እግር ኳስ ትልቅ ተስፋን የሰጠ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል።
የሀገሪቱ ብሔራዊ ቡድንን ውጤት ተከትሎ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ኪንሻሳ ደጋፊዎች ደስታቸውን ገልጸዋል።
በርካታ ደጋፊዎች በመዲናዋ ኪንሻሳ ጎዳናዎች ላይ በመውጣት በደስታ ሲፈነጥዙ ታይተዋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርጅቶ ያልደከመው ሊዮኔል ሜሲ
ከቦንዲ ጎዳናዎች እስከ ፈረንሳይ የታሪክ አናት
ከ4 ሺህ 337 ቀናት በኋላ በአሜሪካ ምድር የሚጫወተው ክርስቲያኖ ሮናልዶ