ኦማር አርታ ከፊፋ ክፍያ ሊፈፀምለት ነው
ሀዋሳ: ሰኔ 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ለመዳኘት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ የተከለከለው ሶማሊያው ዳኛ ኦማር አርታ ከፊፋ ክፍያ ሊፈፀምለት እንደሆነ ተገልጿል።
የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ዳኛ ኦማር አርታ በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በሚኖረው ተሳትፎ ያገኝ የነበረው የገንዘብ እና የጥቅማጥቅም ክፍያዎች ከፊፋ እንደሚከፈለው ተዘግቧል።
የ34 ዓመቱ የእግርኳስ ዳኛ ኦማር አርታን በመጪው ነሃሴ ወር በፒኤስጂ እና በአስቶንቫላ መካከል የሚደረገውን የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ፍፃሜ እንዲመራ መመረጡ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ቶማስ ፓርቴ የዓለም ዋንጫ ቪዛ በመከልከሉ የጋና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የካናዳን መንግስት ወቀሰ
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዝርፊያ ተፈፀመበት
የ2026 የዓለም ዋንጫ፡ የዛሬው የውድድር መርሐግብሮች