የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስ፣ የፈጠራ ስራዎች ውድድርና አውደ ርዕይ መካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ሰኔ 05/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ 3ኛውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስ፣ የፈጠራ ስራዎች ውድድርና አውደ ርዕይ በይፋ አስጀምረዋል።
“ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሣይንስ፣ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ” በሚል መሪ ቃል ለ3ኛ ጊዜ በቡታጅራ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶክተር ባይሳ በዳዳ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ፣ አየለች እሸቴ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም የሳይንስ ኢንፎርሜሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ፣ የስራ እድል ፈጠራ እና ኢንተር ፕራይዝ ልማት ቢሮ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ነው።
በአውደ ርዕዩ ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለህዝብ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ተመላክቷል።
3ኛው የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ውድድር አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የሳይንስ ኢንፎርሜሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ፣ የስራ እድል ፈጠራ እና ኢንተር ፕራይዝ ልማት ቢሮ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ በጋራ ማዘጋጀታቸው ተመልክቷል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)