ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በይርጋጨፌ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን መርቀው ከፈቱ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በይርጋጨፌ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን መርቀው ከፈቱ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድሩ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ከ100 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ 40 ለሚሆኑ የልማት ተነሺዎች እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የተገነቡ ቤቶች፣ በቆንጋ ወንዝ ላይ የተገነባውን ድልድይ፣ የሌማት ትሩፋት መሸጫ ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ