ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በይርጋጨፌ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን መርቀው ከፈቱ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድሩ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ስራዎች ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ከ100 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ 40 ለሚሆኑ የልማት ተነሺዎች እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የተገነቡ ቤቶች፣ በቆንጋ ወንዝ ላይ የተገነባውን ድልድይ፣ የሌማት ትሩፋት መሸጫ ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ