ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ከፈቱ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ከፍተዋል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በብቃት ለመፍታትና የዜጎችን እንግልት መቀነስ የሚያስችለው የመሶብ አገልግሎት ነው ተመርቆ ለስራ ክፍት የሆነው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 3ኛ የሆነውን የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ባጭር ጊዜ ውስጥ በብቃት በማጠናቀቅ ርዕሰ መስተዳድሩ በይፋ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገውታል፡፡
ማዕከሉ 4 የፌዴራል እና 5 የክልል ተቋማት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ስር በማጣመር፤ 32 የተለያዩ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በታገዘ፤ በተቀላጠፈ ዘመናዊ አሰራር በመስጠት ሥራ የሚጀመር ይሆናል።
መሶብ ዜጎች የተሟላ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም በተቀላጠፈ ዘመናዊ አሰራር በቀላሉ የተለያዩ የክልል እና የፌዴራል ተቋማትን አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል አላስፈላጊ ቢሮክራሲን የሚያስቀርና ጊዜና ወጪ ቆጣቢ ኢኒሼቲቭ ነው።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ