በጠምባሮ ልዩ ወረዳ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያ ሆኖ መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጠምባሮ ልዩ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ደጀኔ ለዕመንቾ እንደገለጹት፤ ህዝብ ሲተባበርና ሲደጋገፍ እንዲሁም የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ከፈጠረ የተሻለ ውጤት ይመዘገባል።
ለዚህም የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቁ የህዝቡን አንድነትና አብሮነት አመላካች ነው ብለዋል አቶ ደጀኔ።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ሀብታሙ በላይነህ፤ የሀገር መጪውን ዕድል የሚወስን ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ገልፀው ምርጫው ህብረተሰቡ ዲሞክራሲያዊ መብቱን እንዲያረጋግጥ ያስችላል ብለዋል።
የእለቱ የክብር እንግዳ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ እንደገለጹት፤ ህዝቡ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የክልል፣ የልዩ ወረዳው እና የሙዱላ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና የቀበሌ ካቢኔ አባላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: ጡሚሶ ዳንኤል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ