ምርጫው ነጻ ፍትሀዊ እና ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን በቤንች ሸኮ ዞን በሚዛን ተፈሪ የምርጫ ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራትና የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች ተናገሩ
የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ እና የሲቪክ ማህበራት ፓርቲ ታዛቢዎች መካከል ወይዘሮ አጥናፏ ምትኩ ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን ተወካይ ታዛቢ እና አቶ ዳዊት ዳኜ ከብልጽግና ፓርቲ ተወካይ ታዛቢ እንዲሁም አቶ ጌታሁን ሀይሉ ትብብር ኢትዮጵያ ለአንድነት ፓርቲ ተወካይ ታዛቢ፤ የዘንድሮ ምርጫው ከበፊቱ ለየት የሚያደርገው ከማለዳው አስራ ሁለት ሰአት እስከ ምሽቱ ስድስት ሰአት ህብረተሰቡ በትእግስት ተረጋግቶ ሲመርጥ መታዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።
በምርጫ ሂደቱም ይሁን በቆጠራው ወቅት ያለማንም ጣልቃ ገብነት ምርጫ አስፈጻሚዎች ተግባራቸውን በተገቢው መወጣታቸውን ጠቁመው፤ ከድምጽ አሰጣጡ በኋላ ቆጠራው ተደርጎ ጊዚያዊ ውጤት በተገቢው መለጠፉን መመልከት ችለናል ብለዋል።
በዚህም ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረበ ቅሬታ አለመኖሩን የተናገሩት ታዛቢዎቹ፤ ምርጫው በሰላም ያለምንም የጸጥታ ችግር መጠናቀቁን መታዘብ መቻላቸውንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት በ2018 በጀት ዓመት በኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ከዞኑ ንግድና ትራንስፖርት መምሪያዎች ጋር የህዝብ አስተያየት ማሰባሰቢያ መድረክ አካሄደ
የወጣቶቻችንን ያልተገደበ ምናብ እና የእጆቻቸውን ጥበብ ወደ ተጨባጭ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መቀየር እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስ፣ የፈጠራ ስራዎች ውድድርና አውደ ርዕይ መካሄድ ጀመረ