ምርጫው ነጻ ፍትሀዊ እና ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን በቤንች ሸኮ ዞን በሚዛን ተፈሪ የምርጫ ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራትና የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች ተናገሩ
የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ እና የሲቪክ ማህበራት ፓርቲ ታዛቢዎች መካከል ወይዘሮ አጥናፏ ምትኩ ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን ተወካይ ታዛቢ እና አቶ ዳዊት ዳኜ ከብልጽግና ፓርቲ ተወካይ ታዛቢ እንዲሁም አቶ ጌታሁን ሀይሉ ትብብር ኢትዮጵያ ለአንድነት ፓርቲ ተወካይ ታዛቢ፤ የዘንድሮ ምርጫው ከበፊቱ ለየት የሚያደርገው ከማለዳው አስራ ሁለት ሰአት እስከ ምሽቱ ስድስት ሰአት ህብረተሰቡ በትእግስት ተረጋግቶ ሲመርጥ መታዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።
በምርጫ ሂደቱም ይሁን በቆጠራው ወቅት ያለማንም ጣልቃ ገብነት ምርጫ አስፈጻሚዎች ተግባራቸውን በተገቢው መወጣታቸውን ጠቁመው፤ ከድምጽ አሰጣጡ በኋላ ቆጠራው ተደርጎ ጊዚያዊ ውጤት በተገቢው መለጠፉን መመልከት ችለናል ብለዋል።
በዚህም ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረበ ቅሬታ አለመኖሩን የተናገሩት ታዛቢዎቹ፤ ምርጫው በሰላም ያለምንም የጸጥታ ችግር መጠናቀቁን መታዘብ መቻላቸውንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በዝንጅብል ምርት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለፁ
በሸካ ዞን የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ዴሞክራሲያዊ አሠራር የታየበት ስለመሆኑ ተናገሩ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ