የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ በአርባምንጭ ከተማ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን መታዘብ ችለናል።
የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ በመሆኑ ለሀገሪቱ ሰላም፣ ኢኮኖሚ እና ዴሞክራሲ የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ከራሱ የሚጠበቀውን ሚና መወጣት እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)