የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ ነው – የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች

የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

‎ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል።

‎7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ በአርባምንጭ ከተማ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን መታዘብ ችለናል።

‎የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ በመሆኑ ለሀገሪቱ ሰላም፣ ኢኮኖሚ እና ዴሞክራሲ የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።

‎ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ከራሱ የሚጠበቀውን ሚና መወጣት እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

‎ዘጋቢ፡ ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን