የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ በአርባምንጭ ከተማ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን መታዘብ ችለናል።
የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ በመሆኑ ለሀገሪቱ ሰላም፣ ኢኮኖሚ እና ዴሞክራሲ የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ከራሱ የሚጠበቀውን ሚና መወጣት እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
መብታችንን ተጠቅመን ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል – በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች
“ኢትዮጵያ ትመርጣለች!”
በስልጤ ዞን ላንፉሮ ምርጫ ክልል የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል