መብታችንን ተጠቅመን ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል – በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች
የምርጫ ካርዳቸውን ተጠቅመው ድምጽ ለመስጠት ነገን እየጠበቁ መሆኑን በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
በአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማ ነዋሪነታቸውን ካደረጉ አስተያየት ሰጪዎች መካከል አቶ መልካሙ አንደሞ እና አንድነት ሸሎ፤ የምርጫ ካርዳቸውን አስቀድመው ማውጣታቸውን እና ነገ ግንቦት 24ን በጉጉት በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለሀገር እድገት ይጠቀማል የሚሉትን ፓርቲ በመምረጥ መብታቸውን ለመጠቀም የምርጫውን ቀን በመጠባበቅ ላይ መኾናቸውን አንስተዋል።
ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን መጠቀም አለባቸው ያሉት ደግሞ የሼራ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ፍሬህይወት ካሮ እና የገቲባ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ከበደ ደስታ እንዲሁም ወጣት አሳምነው ታዬ ናቸው።
ከሁሉም ነገር ለሀገር ሠላም ቅድሚያ መስጠት ይገባል ያሉት ነዋሪዎቹ፤ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል።
ምርጫው ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ታሪኩ ታደሰ – ከማሻ ጣቢያችን
መብታችንን ተጠቅመን ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል – በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)