“ኢትዮጵያ ትመርጣለች!”

“ኢትዮጵያ ትመርጣለች!”

ግንቦት 24 ለሚካሄደው ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ እየተሰራጩ መሆናቸውን የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል አስተባባሪ ገለጹ

የምርጫ ክልሉ አስተባባሪ አቶ ኢዮብ አሰፋ፤ በምርጫ ክልሉ በአጠቃላይ 110 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ፣ ጌሻና ከፍል ሳይለም ወረዳዎችን እንደሚያጠቃልል ገልጸዋል።

በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁሶች የማሰራጨት ስራ በስኬት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በደካ ከተማ አስተዳደር የአደባባይ ምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ቢንያም ብርሃኑ እና የጤና ጣቢያ ሰፈር ምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሀይሌ ለምርጫ ማስፈጸሚያ የተላኩ ቁሳቁሶችን መረከባቸውን ተናግረዋል።

ቁሳቁሶቹ ደህንነታቸው በተጠበቀ ቦታ ላይ መቀመጣቸውን የጠቆሙቶ የጣቢያዎቹ ኃላፊዎቹ፤ ለድምፅ መስጫው ዕለት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ታደሰ