በስልጤ ዞን ላንፉሮ ምርጫ ክልል የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል
የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት መጠናቀቁን
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የላንፉሮ ምርጫ ክልል ሀላፊ አቶ ኑረዲን በርጫ ገልፀዋል።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ለማድረግ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የተናገሩት አቶ ኑረዲን፤ በምርጫ ክልሉ 70 ሺህ 258 መራጮች ድምፃቸውን ለመስጠት መመዝገባቸውን ገልፀዋል።
በላንፉሮ ምርጫ ክልል በሚገኙ በሶስቱም ማለትም በሚቶ ወረዳ 25 ፣ በጦራ ከተማ አስተዳደር 16 እንዲሁም በላንፉሮ ወረዳ ደግሞ 36 ምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን በድምሩ 77 ምርጫ ጣቢያዎች እንዲሁም 3 ንዑስ ምርጫ ጣቢያዎች ይገኛሉ ሲሉ ጠቁመዋል።
ኃላፊው በምርጫ በጣቢያዎቹ የቁሳቁስ ስርጭቶች መደረጋቸውን አስታውቀዋል።
ዘጋቢ፡ አለምሸት ግርማ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)