በስልጤ ዞን ላንፉሮ ምርጫ ክልል የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል
የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት መጠናቀቁን
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የላንፉሮ ምርጫ ክልል ሀላፊ አቶ ኑረዲን በርጫ ገልፀዋል።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ ለማድረግ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የተናገሩት አቶ ኑረዲን፤ በምርጫ ክልሉ 70 ሺህ 258 መራጮች ድምፃቸውን ለመስጠት መመዝገባቸውን ገልፀዋል።
በላንፉሮ ምርጫ ክልል በሚገኙ በሶስቱም ማለትም በሚቶ ወረዳ 25 ፣ በጦራ ከተማ አስተዳደር 16 እንዲሁም በላንፉሮ ወረዳ ደግሞ 36 ምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን በድምሩ 77 ምርጫ ጣቢያዎች እንዲሁም 3 ንዑስ ምርጫ ጣቢያዎች ይገኛሉ ሲሉ ጠቁመዋል።
ኃላፊው በምርጫ በጣቢያዎቹ የቁሳቁስ ስርጭቶች መደረጋቸውን አስታውቀዋል።
ዘጋቢ፡ አለምሸት ግርማ

More Stories
መብታችንን ተጠቅመን ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል – በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች
“ኢትዮጵያ ትመርጣለች!”
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከምባታ ዞን 5 የምርጫ ክልሎች ያሉ ሲሆን ከእነዚያ አንዱ የሆነው የቀዲዳ ጋሜላ-02 የምርጫ ክልል ለምርጫ ጣቢያዎች የቁሳቁስ ስርጭት እያደረገ ይገኛል