በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ
ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ነገን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር መንግሥት ለመምረጥ ዕለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ከይርጋጨፌ ነዋሪዎች አቶ አክሊሉ መኩሪያ፣ ወ/ሮ የኔነሽ ባሬ እና ሌሎችም ተናግረዋል፡፡
የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በማስቀመጥ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ዴሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም ለሚያምኑት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡
በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ መሆኑን በመረዳት እንዳይባክን ጥንቃቄ በማድረግ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

More Stories
መብታችንን ተጠቅመን ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል – በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ነዋሪዎች
“ኢትዮጵያ ትመርጣለች!”
በስልጤ ዞን ላንፉሮ ምርጫ ክልል የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል