‎በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

‎በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

‎ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ነገን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር መንግሥት ለመምረጥ ዕለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ከይርጋጨፌ ነዋሪዎች አቶ አክሊሉ መኩሪያ፣ ወ/ሮ የኔነሽ ባሬ እና ሌሎችም ተናግረዋል፡፡

‎የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በማስቀመጥ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ዴሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም ለሚያምኑት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡

‎በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ መሆኑን በመረዳት እንዳይባክን ጥንቃቄ በማድረግ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡

‎ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን