በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ
ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ነገን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር መንግሥት ለመምረጥ ዕለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ከይርጋጨፌ ነዋሪዎች አቶ አክሊሉ መኩሪያ፣ ወ/ሮ የኔነሽ ባሬ እና ሌሎችም ተናግረዋል፡፡
የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በማስቀመጥ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ዴሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም ለሚያምኑት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡
በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ ለቀጣይ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ መሆኑን በመረዳት እንዳይባክን ጥንቃቄ በማድረግ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)