በአንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ለምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች እየተሰራጩ መሆኑ ተገለፀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ቁሳቁሶች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጩ ይገኛል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ ሰላሙ ማርቆስ፤ በምርጫ ክልሉ 61 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በየምርጫ ጣቢያው በትላንትናው እለት 53 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሰራጩ ገልጸው፤ 10 የምርጫ ጣቢያዎች አሁን እያሰራጩ መሆኑን ነው የገለጹት።
አቶ ሰላሙ እንደተናገሩት፤ ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ አንገጫ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል 50 ሺህ 3 መቶ 11 ድምጽ ለመስጠት መራጮች እንደተመዘገቡ ጠቁመዋል።
ዘጋቢ: ሐና በቀለ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)