በአንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ለምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች እየተሰራጩ መሆኑ ተገለፀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ቁሳቁሶች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጩ ይገኛል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ ሰላሙ ማርቆስ፤ በምርጫ ክልሉ 61 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በየምርጫ ጣቢያው በትላንትናው እለት 53 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሰራጩ ገልጸው፤ 10 የምርጫ ጣቢያዎች አሁን እያሰራጩ መሆኑን ነው የገለጹት።
አቶ ሰላሙ እንደተናገሩት፤ ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ አንገጫ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል 50 ሺህ 3 መቶ 11 ድምጽ ለመስጠት መራጮች እንደተመዘገቡ ጠቁመዋል።
ዘጋቢ: ሐና በቀለ

More Stories
በእጃችን ያለው የምርጫ ካርድ እንዳይባክን የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ
ማህበረሰቡ የምርጫውን እለት በመዘንጋት የመምረጥ እድሉን እንዳያሳልፍ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በሆሳዕና ከተማ እየተሰራ ነው
“ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል” – የቢጣ ገነት ከተማ ነዋሪዎች