“ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል” – የቢጣ ገነት ከተማ ነዋሪዎች
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ይካሄዳል፡፡
ጣቢያችን በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ቢጣ-ገነት ከተማ ተገኝቶ የከተማዋን ነዋሪዎች አነጋግሯል፡፡
ካነጋገርናቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ተረፈ ከበደ፣ አቶ ሙሉጌታ ዘውዴ፣ ወይዘሮ አለሚቱ ሃይሌ፣ ወጣት ምንላርግህ ቆጭቶ እና ወጣት ዘውዲቱ አምቦ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅት አጠናቀው ቀኑን እየጠበቁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ይበጀናል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችለንን ካርድ በመውሰድ ቀኑን በጉጉት በመጠበቅ ላይ እንገኛለን ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ከምርጫው ጎን ለጎን የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንደሚገባም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)