በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለጸ

በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለጸ

‎ግንቦት 24/2018 ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ የማሰራጨቱን ስራ እያጠናቀቀ መሆኑን የምርጫ ክልሉ አስተባባሪው ተናግረዋል።

‎በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል መደበኛ 84 የምርጫ ጣቢያዎች እና 2 ንዑስ እንዲሁም 6 ሀገር አቀፍ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚፎካከሩባቸው የምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ መሆኑን የምርጫ ክልሉ አስተባባሪው ተናግረዋል።

‎የመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ አራታ በተላ፤ እስካሁን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች ስርጭት መከናወኑን ገልጸዋል፡፡

‎ቀሪውን የቁሳቁስ ስርጭት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡

‎የፀጥታ አካላት ከፀጥታና ደህንነት ጥበቃ በተጨማሪ በቁሳቁስ ስርጭት ወቅት አስፈላጊውን እጀባ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

‎ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ጣቢያችን