በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለጸ
ግንቦት 24/2018 ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ የማሰራጨቱን ስራ እያጠናቀቀ መሆኑን የምርጫ ክልሉ አስተባባሪው ተናግረዋል።
በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል መደበኛ 84 የምርጫ ጣቢያዎች እና 2 ንዑስ እንዲሁም 6 ሀገር አቀፍ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚፎካከሩባቸው የምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ መሆኑን የምርጫ ክልሉ አስተባባሪው ተናግረዋል።
የመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ አራታ በተላ፤ እስካሁን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች ስርጭት መከናወኑን ገልጸዋል፡፡
ቀሪውን የቁሳቁስ ስርጭት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡
የፀጥታ አካላት ከፀጥታና ደህንነት ጥበቃ በተጨማሪ በቁሳቁስ ስርጭት ወቅት አስፈላጊውን እጀባ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።
ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ጣቢያችን
በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደየምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለጸ

More Stories
በአንገጫ ቁጥር 1 የምርጫ ክልል ለምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች እየተሰራጩ መሆኑ ተገለፀ
ማህበረሰቡ የምርጫውን እለት በመዘንጋት የመምረጥ እድሉን እንዳያሳልፍ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በሆሳዕና ከተማ እየተሰራ ነው
“ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል” – የቢጣ ገነት ከተማ ነዋሪዎች