ለድምጻችን ዋጋ በመስጠት ነገ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚበጀንን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የቢይራሌ ከተማ ነዋሪዎች
ሀዋሳ: 23/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለድምጻችን ዋጋ በመስጠት ነገ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚበጀንን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ የቢይራሌ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
በወረዳው ቢራይሌ ከተማ የደቡብ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋዜጠኞች ጋር ቆይታ ያደረጉት አስተያየት ሰጪዎች እንደገለፁት፥ ሰኞ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፣ ልማትና መልካም አሰተዳደር ያረጋግጥልኛል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
የከተማ ነዋሪዎቹ አክለውም ምርጫ የተሻለ ሀገርን ለመገንባት እና የሰለጠነ ዴሞክራሲ መገለጫ በመሆኑ በዕለቱ ካርዱን ይዞ መብቱን እንዲጠቀም አሳስበዋል።
የአንድ ሰው ድምጽ ዋጋ እንዳለው በማመን ምርጫው ሠላማዊ ፣ ዲሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ: አርሻል አራቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)