ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ ከያዙ ቤተሰቦቻቸው ጋር በንቃት እየተጠባበቁ መሆናቸውን የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ

ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ ከያዙ ቤተሰቦቻቸው ጋር በንቃት እየተጠባበቁ መሆናቸውን የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ

ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

ከዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብቶች አንዱ ምርጫ ነው ያሉት የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች፤ ነገ ሰኞ በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ ከያዙ ቤተሰቦቻቸው ጋር በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተቀመጠው የጊዜ ሳሌዳ መሰረት ባለፉት ጊዜያት ለፓርቲዎች በተዘጋጀው የክርክር መድረክ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያቀረቡትን ሀሳብ በንቃት መከታተላቸው ለምርጫ ተሳትፏቸው መልካም ድባብ እንደፈጠረላቸው ጠቅሰው፤ በዚህም ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።

የሰላም ባለቤት ህዝቡ ነው ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸው ድርሻ እንደሚወጡ ገልፀው ሁሉም ለሰላም ዘብ መቆም እንዳለበትም ገልጸዋል።

የምርጫ ካርድ የወሰዱ ዜጎችም በምርጫው ዕለት ይመራኛል የሚሉትን ፓርቲ በነፃነት በመምረጥ መንግስት የመመስረት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም አስተያየት ሰጪዎቹ ምክረ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል።

ዘጋቢ፡ ኤደን ተረፈ አና ኤርጡሜ ዳንኤል – ከሆሳዕና ጣቢያችን