ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የደካ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የደካ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ

ምርጫ ለአንድ ሀገር ዴሞክራሲ መጎልበትና ሉዓላዊነት ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

ጣቢያችን ሁነቱን እየተከታተለ ለመዘገብ በስፍራው የተገኘ ሲሆን በዚህ ወቅት ያነጋገርናቸው የደካ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለፁት፤ ዜጎች ምርጫ ላይ በነቂስ መሳተፋቸው የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው።

በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ እንደሆኑም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ምርጫ የዴሞክራሲ መገለጫና ሀገርን የሚያስቀጥል ሥርዓት እንደሆነም ተናግረዋል።

የወሰዱትን የመራጭነት ካርድ በጥንቃቄ ይዘው መቆየታቸውን የተናገሩት ነዋሪዎቹ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ማልደው በመነሳት ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፤ ልማትና ዕድገት ያረጋግጣል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስተያየት ሰጭዎቹ ተናግረዋል።

ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የአንድ ሰው ድምፅ ትልቅ ዋጋ እንዳለው በመገንዘብ፣ ካርድ የወሰደ ዜጋ ሁሉም በዕለቱ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል።

ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ታደሰ

ፎቶ፡ ኪዳኔ ተስፋዬ