ወጣቱን ተጠቃሚ ያደርጋል ያልነውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የሶያማ ከተማ ወጣቶች

ወጣቱን ተጠቃሚ ያደርጋል ያልነውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የሶያማ ከተማ ወጣቶች

‎ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለወደፊቱ ይበጀናል ያልነውን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በቡርጂ ዞን የሶያማ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ።

‎በሶያማ ከተማ አስተዳደር የ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወጣት ማሻ ማርቻ እና ህርቦ አለማየሁ ለሀገራችን ልማት እና እድገት ይጠቅመናል የምንለውን ለመምረጥ ዝግጅት አድርገናል ሲሉ ተናግረዋል።

‎በከተማው የ 02 ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወጣት ጥሩዬ ካሳ የእኔ አንድ ድምጽ ያለው ዋጋ ቀላል ባለመሆኑ የመምረጥ መብቴን በመጠቀም የሚያስተዳድረኝን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ስትል ገልጻለች።

‎ሌላኛው አስተያየታቸውን የሰጡን የኦቶማሎ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ህርብቻ ዋዮ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብዬ የማስበውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብሏል።

‎አስተያየት ሰጪዎቹ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ሀሳባቸውን አጋርተዋል።


‎ዘጋቢ: አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን