ወጣቱን ተጠቃሚ ያደርጋል ያልነውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የሶያማ ከተማ ወጣቶች
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለወደፊቱ ይበጀናል ያልነውን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በቡርጂ ዞን የሶያማ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ።
በሶያማ ከተማ አስተዳደር የ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወጣት ማሻ ማርቻ እና ህርቦ አለማየሁ ለሀገራችን ልማት እና እድገት ይጠቅመናል የምንለውን ለመምረጥ ዝግጅት አድርገናል ሲሉ ተናግረዋል።
በከተማው የ 02 ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወጣት ጥሩዬ ካሳ የእኔ አንድ ድምጽ ያለው ዋጋ ቀላል ባለመሆኑ የመምረጥ መብቴን በመጠቀም የሚያስተዳድረኝን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ስትል ገልጻለች።
ሌላኛው አስተያየታቸውን የሰጡን የኦቶማሎ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ህርብቻ ዋዮ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብዬ የማስበውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብሏል።
አስተያየት ሰጪዎቹ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ሀሳባቸውን አጋርተዋል።
ዘጋቢ: አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ወጣቱን ተጠቃሚ ያደርጋል ያልነውን መንግስት ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የሶያማ ከተማ ወጣቶች

More Stories
ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ ከያዙ ቤተሰቦቻቸው ጋር በንቃት እየተጠባበቁ መሆናቸውን የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የደካ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ