የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች

የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች

ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አንዳንድ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊ እና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ፤ በእለቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ሰዓቱንና ስርአቱን ጠብቀው የድርሻውን መወጣት እንዳለባቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ምርጫ ዜጎች ለነገዋ ኢትዮጵያ ስኬት በተሻለ ይሰራል ብለው ያሰቡትን የመምረጥ እና የራሳቸውን እድል በራሳቸው የመወሰን መብታቸውን የሚያስከብሩበት ሂደት መሆኑንም ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት አንስተዋል።

ዘጋቢ፡ ሸዊት ሂርጶ