የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በመጠቀም ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አንዳንድ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊ እና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ፤ በእለቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ሰዓቱንና ስርአቱን ጠብቀው የድርሻውን መወጣት እንዳለባቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ምርጫ ዜጎች ለነገዋ ኢትዮጵያ ስኬት በተሻለ ይሰራል ብለው ያሰቡትን የመምረጥ እና የራሳቸውን እድል በራሳቸው የመወሰን መብታቸውን የሚያስከብሩበት ሂደት መሆኑንም ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ሸዊት ሂርጶ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)