የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የማሻ ከተማ ነዋሪዎች
ይበጀኛል፣ ትዉልድን ያሻግራል እንዲሁም ሀገርን ይመራል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸዉን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን የማሻ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
ነዋሪዎቹ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ የዜጎች ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸው፤ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማካሄድ የሀገሪቱን ሠላም፣ ልማትና አንድነት የሚያስቀጥል የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ በካርዳቸዉ ይበጀኛል፣ ትዉልድን ያሻግራል እንዲሁም ሀገርን ይመራል ላሉት ፓርቲ ድምጻቸውን እንደሚሰጡም ገልጸዋል።
የድምጽ መስጫዉ ዕለት ዜጎች ድምጻቸዉን ለሚፈልጉት ፓርቲ መስጠት እንዳለባቸዉ ያነሱት የማሻ ከተማ ነዋሪዎች፤
ምርጫዉ በሠላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ እንደ ዜጋ የድርሻቸዉን እንደሚወጡም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ግርማ ጮሪቶ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
የሀዋሳ ከተማ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል