የሀዋሳ ከተማ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል

የሀዋሳ ከተማ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል

የድምፅ መስጫ ቁሳቁሶች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የማድረስ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት የሀዋሳ ከተማ የምርጫ ክልል ኃላፊ ወ/ሪት ከፊቱ ስዩም፤ በከተማዉ 308 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን እስከአሁን በ259 ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ መስራጨቱን አስታዉቀዋል።

ለቀሪ 49 የምርጫ ጣቢያዎች በነገዉ እለት እንደሚሰራጭም ተናግረዋል።

ኃላፊዋ አክለዉም፤ በስርጭት ወቅት ችግሮች እንዳይገጥሙ ከፖሊስ አካላት ጋር የቅንጅት ስራ መስራቱንም ገልጸዋል።

ዘጋቢ፡ ባየሽ ጉልላት