የሀዋሳ ከተማ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል
የድምፅ መስጫ ቁሳቁሶች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የማድረስ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት የሀዋሳ ከተማ የምርጫ ክልል ኃላፊ ወ/ሪት ከፊቱ ስዩም፤ በከተማዉ 308 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን እስከአሁን በ259 ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ መስራጨቱን አስታዉቀዋል።
ለቀሪ 49 የምርጫ ጣቢያዎች በነገዉ እለት እንደሚሰራጭም ተናግረዋል።
ኃላፊዋ አክለዉም፤ በስርጭት ወቅት ችግሮች እንዳይገጥሙ ከፖሊስ አካላት ጋር የቅንጅት ስራ መስራቱንም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ባየሽ ጉልላት

More Stories
በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የማሻ ከተማ ነዋሪዎች