አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁሶች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለፀ
በምርጫ ክልሉ ለሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊ ቁሳቁሶች እየተሰራጩ መሆኑን የሶዶ ዙሪያ 2 ምርጫ ክልል ኃላፊ አስታወቁ።
ኃላፊው ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሥርጭቱን በማከናወናቸው ምንም ዓይነት ችግር እንዳልገጠማቸው ጠቁመዋል።
የሶዶ ዙሪያ 2 ምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ ምህረቱ ጋዴቦ በምርጫ ክልሉ 108 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ገልፀው፤ ለሁሉም በሚባል ደረጃ አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁስ መሰራጨቱን ገልፀዋል።
በምርጫ ክልሉ ከሚገኙ 108 ጣቢያዎች ውስጥ በ92ቱ የመራጮች ምዝገባ ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል መከናወኑን ጠቅሰው፤ በቀሪ 16ቱ በማኑዋል መመዝገቡን አስታውቀዋል።
ለሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊ ቁሳቁስ በማሰራጨት የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል ያሉት አቶ ምህረቱ፥ የፀጥታ አካላት ኃላፊነታቸውን መወጣታቸው ሥራው በስኬት እንዲጠናቀቅ ማድረጉን ጠቁመዋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፋና ቀበሌ ዲያስፖራ መንደር ጉጃ ኮይራ ምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ አዲሱ ጎአ በበኩላቸው ለምርጫ ጣቢያው የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን መረከባቸውን ተናግረዋል።
ርክክቡን የፀጥታ አካላትን ጨምሮ መገኘት ካለባቸው አካላት ጋር በጋራ ማከናወናቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ካሱ ብርሃኑ

More Stories
የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የማሻ ከተማ ነዋሪዎች
የሀዋሳ ከተማ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል