በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

‎ስልጣን በሠላማዊ መንገድና በዜጎች የነቃ ተሳትፎ በሚደረግ የድምጽ አሰጣጥ የምርጫ ስርዓት የሚገኝ መሆኑን አንዳንድ መራጮች በሰጡት አስተያዬት ገልጸዋል።

‎ውሳኔአቸውን በድምፃቸው እንደሚያረጋግጡ የተናገሩት ነዋሪዎቹ፥ ምርጫ መብትና የዜግነት ግዴታ በመሆኑ የወሰዱትን ካርድ ጥቅም ላይ ለማዋል በምርጫው እንደሚሳተፉም ተናግረዋል።

‎ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ነዋሪዎቹ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በሰጡት አስተያዬት አመላክተዋል።

‎ዘጋቢ: ቅድስት ዳንኤል