አርሰናል ክርስቶስ ዞሊስን ለማስፈረም ተስማማ

አርሰናል ክርስቶስ ዞሊስን ለማስፈረም ተስማማ

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመስመር አጥቂውን ክርስቶስ ዞሊስን ከክለብ ብሩጅ ለማስፈረም ከስምምነት ላይ ደርሷል።

መድፈኞቹ ለግሪካዊው ተጫዋች ዝውውር 40 ሚሊዮን ዩሮ ሒሳብ ለመክፈል መስማማታቸው ተገልጿል።

የ24 ዓመቱ ተጫዋች ክርስቶስ ዞሊስ አርሰናልን ለቆ ወደ ቤሺክታሽ ለተዛወረው ሊያንድሮ ትሮሳርድ ሁነኛ ተተኪ ይሆናል ተብሎ ይታሰባል።

ክርስቶስ ዞሊስ ከሦስት ዓመታት በፊት በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ለኖርዊች ሲቲ ተጫውቶ ማሳለፉ የሚዘነጋ አይደለም።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ