በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሌሞ 01 ምርጫ ክልል ስር ለሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ስርጭት እየተደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሌሞ 01 ምርጫ ክልል ስር ለሚገኙ 140 የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ስርጭት እያከናወነ መሆኑን የሌሞ 01 ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ ሙሉቀን አሻግሬ ገለፁ።
በሌሞ 01 ምርጫ ክልል ስር 140 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ የገለፁት አስተባባሪው፤ የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ስርጭቱን በተሳካ ሁኔታ ለማሳለጥ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙም አብራርተዋል።
በምርጫ ጣቢያዎቹ 125,548 መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የጠቆሙት አስተባባሪው፤ 62,500 የሚሆኑት መራጮች በዲጂታል አማራጭ የተመዘገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሌሞ ወረዳ የደማላ ባልቡላ ምርጫ ጣቢያ ትምህርት ቤት የምርጫ ጣቢያው ሀላፊ አቶ ጥጋቡ ታፈሰ፤ ለምርጫ ጣቢያው የሚሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን ለመረከብ በስፍራው መገኘታቸውን ጠቅሰው፤ የምርጫ ክልሉ ቁሳቁሶችን በጊዜ ተደራሽ የማድረግ ስራውን በተገቢው ሁኔታ እያካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ሸዊት ሂርጶ

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)