በዕለቱ ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ ይገባል – የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች
በምርጫዉ ዕለት ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ እንደሚገባ በሀዲያ ዞን የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ ከዚህ በፊትም በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ካርድ መውሰዳቸውን ገልፀው፤ በዕለቱ ተገኝተው ለመምረጥ ዝግጅታቸውን ጨርሰው በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ከአሁን በፊት የተካሄዱትን የፖለቲካ ፖርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ በንቃት ሲከታተሉ እንደነበር አስታዉሰዋል።
የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ለይኩን ሱልዶሎ በበኩላቸዉ፤ ዴሞክራሲያዊና አሳታፊ ብሎም ቅቡልነት ያለዉ ምርጫ እንዲሆን ቅድመ ዝግጅቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ሰኞ የገበያ ዕለት ቢሆንም እንዳይኖሮ ዝግ መደረጉን የገለፁት ከንቲባው፤ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችም ከቁሳቁስ ጀምሮ ሌሎችም አስፈላጊ ግብአቶች መሟላታቸውን አመላክተዋል።
በዕለቱ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ካርድ የወሰዱ መራጮች በሙሉ በምርጫ ጣቢያቸው ተገኝተዉ ይሆነኛል ብለዉ ለሚያምኑትን የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ በመስጠት እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ
በዕለቱ ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ ይገባል – የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)