‎‎በዕለቱ ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ ይገባል – የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች

‎‎በዕለቱ ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ ይገባል – የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች

‎በምርጫዉ ዕለት ህብረተሰቡ ቀጣይ ሀገሬን በስኬትና ከፍታ ማን ሊመራ ይገባል የሚለዉን አፅንዖት በመስጠት ድምፅ ሊሰጥ እንደሚገባ በሀዲያ ዞን የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናግረዋል።

‎ነዋሪዎቹ ከዚህ በፊትም በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ካርድ መውሰዳቸውን ገልፀው፤ በዕለቱ ተገኝተው ለመምረጥ ዝግጅታቸውን ጨርሰው በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

‎ከአሁን በፊት የተካሄዱትን የፖለቲካ ፖርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ በንቃት ሲከታተሉ እንደነበር አስታዉሰዋል።

‎የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ለይኩን ሱልዶሎ በበኩላቸዉ፤ ዴሞክራሲያዊና አሳታፊ ብሎም ቅቡልነት ያለዉ ምርጫ እንዲሆን ቅድመ ዝግጅቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎በከተማ አስተዳደሩ ሰኞ የገበያ ዕለት ቢሆንም እንዳይኖሮ ዝግ መደረጉን የገለፁት ከንቲባው፤ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችም ከቁሳቁስ ጀምሮ ሌሎችም አስፈላጊ ግብአቶች መሟላታቸውን አመላክተዋል።

‎በዕለቱ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ካርድ የወሰዱ መራጮች በሙሉ በምርጫ ጣቢያቸው ተገኝተዉ ይሆነኛል ብለዉ ለሚያምኑትን የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ በመስጠት እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።
‎ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ