ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶችን ለምርጫ ጣቢያዎች እያሰራጨ መሆኑን የአማሮ ኬሌ ምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት አሰታወቀ

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶችን ለምርጫ ጣቢያዎች እያሰራጨ መሆኑን የአማሮ ኬሌ ምርጫ ክልል ጽህፈት ቤት አሰታወቀ


በምርጫ ክልሉ ከ87 ሺህ በላይ መራጮች ተመዝግበው ካርድ መውሰዳቸው ተመላክቷል፡፡

‎የአማሮ ኬሌ ምርጫ ክልል ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተካበ ቦጋለ እንደተናገሩት፤ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አቅጣጫ መነሻ ከመራጮች ምዝገባ አንስቶ በምርጫ ክልሉ በቂ ዝግጅት ተደርጓል።

‎አስፈላጊ ቁሳቁሶች ለምርጫ ክልሉ መላካቸውን የተናገሩት ኃላፊው፤ አሁን ላይ የምርጫ ቁሳቁሶችን ለመምርጫ ጣቢያዎች እያሰራጩ እንደሆነ አመላክተዋል።

‎በአማሮ ኬሌ ምርጫ ክልል 1 መቶ 17 ምርጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን በጣቢያዎቹ 87 ሺህ 1 መቶ 1 መራጮች ተመዝግበው ካርድ መውሰዳቸውንም ገልጸዋል።

‎ከተመዘገቡ መራጮች መካከል 44 ሺህ 6 መቶ 68 ወንዶች ሲሆኑ 42 ሺህ 5 መቶ 6 ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን አቶ ተካበ ተናግረዋል።

‎ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ከ54 ሚሊየን በላይ መራጮች መመዝገባቸው ይታወቃል።

‎ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን