‎‎‎የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ዞን አቀፍ ማጠቃለያ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እየተካሄደ ነው

‎‎‎የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ዞን አቀፍ ማጠቃለያ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እየተካሄደ ነው

‎በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ዞን አቀፍ ማጠቃለያ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል።

‎7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሸካ ዋና መቀመጫ በሆነችው ቴፒ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በነቂስ በመውጣት ለፓርቲው ያለቸውን ድጋፍ ገልፀዋል።

‎የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ጎዳና የጀመረችውን ጉዞ የምታጸናበት ነው፣ በመደመር እሳቤ ወደ ብልጽግና፣ ብልጽግና ጉዞ በህዝብ ይሁንታ ይቀጥላል፣ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር፣ የሚሉትንና ሌሎች መፎክሮችን በሰልፉ ላይ ደጋፊዎች አሰምተዋል።

‎ዘጋቢ፡ ታሪኩ ታደሰ – ከሸካ ጣቢያችን