ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በተገኙበት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሠልፍ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ከየወረዳው የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሠልፉ ተሣትፈዋል።
በሠልፉ ላይ የፓርቲው የምርጫ ምልክት “የስንዴ ነዶ” ምስል አእንዲሁም የተለያዩ መፈክሮች እየተስተጋቡ ይገኛሉ።
የፈረስ ጉግስ፣ የባህላዊ መሣሪያዎች ጨዋታ፣ ስፖርት ትርዒት እና የመሳሰሉ ሁነቶችም የሰልፉ ድምቀት ሆነው ታይተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ታርጫ ብዝሃ ከተማ እየተካሄደ ባለው የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ሠልፍ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)