ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በተገኙበት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሠልፍ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ከየወረዳው የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሠልፉ ተሣትፈዋል።
በሠልፉ ላይ የፓርቲው የምርጫ ምልክት “የስንዴ ነዶ” ምስል አእንዲሁም የተለያዩ መፈክሮች እየተስተጋቡ ይገኛሉ።
የፈረስ ጉግስ፣ የባህላዊ መሣሪያዎች ጨዋታ፣ ስፖርት ትርዒት እና የመሳሰሉ ሁነቶችም የሰልፉ ድምቀት ሆነው ታይተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ታርጫ ብዝሃ ከተማ እየተካሄደ ባለው የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ሠልፍ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም ከተሞችን ፅዱና ምቹ ከማድረግ ባሻገር የኤክስፖርት ምርትን ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ገለጸ
ወጣቶች የፊታችን ግንቦት ወር በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የዲሞክራሲ ባህል ማሳደግ እንደሚገባቸው በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለተመራቂ ተማሪዎቹ የተሻለ የስራ እድልና መነሳሳት ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገለፀ