በኣሪ ዞን ሰሜን አሪ ወረዳ የራጺ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነች
ከተማዋን ከቀበሌ የሚያገናኝ የ10 ኪሎ ሜትር የገጠር መንገድም በይፋ ተመርቋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው የአመራሮች ቡድን በኣሪ ዞን የሰሜን አሪ ወረዳ የጀመረው የስራ ጉብኝት እንደቀጠለ ይገኛል።
በሁለተኛው ቀን የስራ ጉብኝታቸው ዋና አፈ ጉባኤው አቶ አለማየሁ ባዲ ከመሩት የአመራር ቡድን ጋር የተገኙት በዞኑ ሰሜን አሪ ወረዳ አርፋሮ ክላስተር በራጺ ታዳጊ ማዘጋጃ ከተማ ነው።
በከተማው የዘመናት የህዝብ ጥያቄ ምንጭ የነበሩ የመንገድና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመመረቅ በይፋ አስጀምረዋል።
በዚህም ከተማዋ የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ መብራት አገልግሎት ተጠቀሚ መሆኗ በይፋ የተረጋገጠ ሲሆን በተመሳሳይ በአርፋሮ አካባቢ የሚገኘው የባዘራ – ራፂ 10 ኪሎ ሜትር መንገድንም መርቀው ከፍተዋል።
የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የወረዳው የአካባቢው ነዋሪዎች በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ደስታቸውን ሲገልጹ ተስተውለዋል።
ነዋሪዎቹም የዘመናት ጥያቄያቸው መልስ ያገኘበት ታሪካዊ ዕለት በመሆኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ወንድሜነህ አድማሱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ያነጋገርናቸው አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ
በምርጫ ጊዜ የሚነሱ ችግሮችን በገለልተኝነትና በህግ አግባብ ብቻ ለመፍታት የፍትህ አካላት ሚና የላቀ መሆኑ ተጠቆመ