ጤናን ለመጠበቅም ሆነ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጎልበት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ትኩረት ሊሰጠዉ እንደሚገባ ተመላከተ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ ጤናዬን እጠብቃለሁ ምርጫን እመርጣለሁ በሚል መሪ ሃሳብ ህዝባዊ የስፖርት እንቅስቃሴና ዉድድር ተካሂዷል።
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ዘርሁን አሰፋ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ንግግራቸዉ እንደገለጹት፤ ስፖርት በርካታ ዜጎችን በአንድነት የሚያሰባስብ የፍቅር መድረክ በመሆኑ በተለይ ወጣቱ ትዉልድ የራሱን ጤና በመጠበቅ የሃገርን ሠላም ለማጽናት ብርቱ ትግል ማድረግ ይጠበቃል።
የወረዳዉ ህዝብ በስፖርት ሜዳው ያሳየዉን አንድነት ሠላማዊ ምርጫን በማካሄዱ ሂደትም በንቃት እንዲሳተፍ ኃላፊው አሳስበዋል።
የወረዳዉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸው ጥላሁን፤ በወረዳው በሚገኙ ሁሉም ማዕከላት መሰል መርሃ-ግብሮችን በማካሄድ ጤናን ከመጠበቅ በተጓዳኝ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ከተሳተፉት መካከል አቶ አበራ አሰፋና መልካሙ ታደለ፤ በስፖርቱ በመሳተፋቸው እንዳስደሰታቸው ገልጸዉ በስፖርት ሜዳ ያሳዩትን አንድነት በጠቅላላ ምርጫውም እንደሚደግሙት ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ጤናን ለመጠበቅም ሆነ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጎልበት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ትኩረት ሊሰጠዉ እንደሚገባ ተመላከተ

More Stories
የነበሩ ችግሮች እየተቀረፉ በመምጣታቸው የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን በከምባታ ዞን አንዳንድ የዶዮገና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተገልጋዮች ተናገሩ
የህብረተሰቡን የግልና አካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ባህል ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ
የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሉት ተደራሽነትና የተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ መምጣቱን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ገለፀ