ሀገራዊ ለውጡ ዕውን የሆነበት 8ኛ ዓመት እና የብልጽግና ፓርቲ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ምረቃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ቂልጦ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ሀገራዊ ለውጡ ዕውን የሆነበት 8ኛ ዓመት እና የብልጽግና ፓርቲ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ምረቃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ቂልጦ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል

በፕሮግራሙ በወረዳው ቂልጦ ከተማ የተገነቡ ከ41 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ይመረቃሉ።

በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ የክልልና የዞን የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የብልጽግና ፓርቲ የአካባቢው ዕጩዎችና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል በመላው ሀገሪቱ እየተካሄደ የሚገኘው የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ፤ ብልጽግናን እመርጣለሁ፤ አሻራዬን አኖራለሁ፣ ከብልጽግና ጋር መጪው ጊዜ የከፍታ ነው፣ ብልጽግናን መምረጥ የኢትዮጵያን ከፍታ ማረጋገጥ ነው የሚሉና ሌሌች መፈክሮች ተስተጋብተዋል።

ዘጋቢ: ሙጂብ ጁሃር – ከሆሳዕና ጣቢያችን