የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደው አለም አቀፍ ኮንፍረንስ ጀመረ
የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዳዊት ሀዬሶ ዶ/ር በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት የሰላም አምባሳደር የሆነው የዋቸሞ የዩቨርሲቲ ከመማር ማስተማር በተጨማሪ በማህበረሰብ አገልግሎት ብሎም በምርምርና ጥናት ስራዎች ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።
ዩኒቨርሲቲውን የምርምር ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ፕሬዝደንቱ፥ ዩኒቨርሲቲው ከዋና ማዕከሉ በተጨማሪ ባሉት ካምፓሶቹ በሁሉ አቀፍ ዘርፎች በርካታ ልማታዊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ኮንፈረንሱ ከሚያዝያ 29-30/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላትና የሥራ ኃላፊዎች፣ አለም አቀፍ ተመራማሪዎች ዳይሬክተሮችና እና ሌሎች እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የበቆሎ ምርጥ ዘር በወቅቱ በማግኘታቸው ትኩረታቸውን የእርሻ ዝግጅት ላይ እንዲያደርጉ እንዳስቻላቸው በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ
ከወላይታ ዞንና ሶዶ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የወጣቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ አድርገዋል
ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዜጎችን የመልማት ፍላጎት ደረጃ በደረጃ በመመለስ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለጸ