የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደው አለም አቀፍ ኮንፍረንስ ጀመረ
የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዳዊት ሀዬሶ ዶ/ር በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት የሰላም አምባሳደር የሆነው የዋቸሞ የዩቨርሲቲ ከመማር ማስተማር በተጨማሪ በማህበረሰብ አገልግሎት ብሎም በምርምርና ጥናት ስራዎች ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።
ዩኒቨርሲቲውን የምርምር ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ፕሬዝደንቱ፥ ዩኒቨርሲቲው ከዋና ማዕከሉ በተጨማሪ ባሉት ካምፓሶቹ በሁሉ አቀፍ ዘርፎች በርካታ ልማታዊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ኮንፈረንሱ ከሚያዝያ 29-30/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላትና የሥራ ኃላፊዎች፣ አለም አቀፍ ተመራማሪዎች ዳይሬክተሮችና እና ሌሎች እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ