የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደው አለም አቀፍ ኮንፍረንስ ጀመረ
የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዳዊት ሀዬሶ ዶ/ር በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት የሰላም አምባሳደር የሆነው የዋቸሞ የዩቨርሲቲ ከመማር ማስተማር በተጨማሪ በማህበረሰብ አገልግሎት ብሎም በምርምርና ጥናት ስራዎች ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።
ዩኒቨርሲቲውን የምርምር ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ፕሬዝደንቱ፥ ዩኒቨርሲቲው ከዋና ማዕከሉ በተጨማሪ ባሉት ካምፓሶቹ በሁሉ አቀፍ ዘርፎች በርካታ ልማታዊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ኮንፈረንሱ ከሚያዝያ 29-30/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላትና የሥራ ኃላፊዎች፣ አለም አቀፍ ተመራማሪዎች ዳይሬክተሮችና እና ሌሎች እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል
የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምክር ቤቶች ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ማከናወን እንደሚገባቸው የኮንሶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ገለጸ
የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ አሳታፊ እና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ