ከወላይታ ዞንና ሶዶ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የወጣቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ አድርገዋል

ከወላይታ ዞንና ሶዶ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የወጣቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ አድርገዋል

በሰልፉ የተገኙት የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ አፀደ አይዛ፤ ወጣቱ የብልፅግና ዕሳቤን በመያዝ አሰባሳቢ ገዢ ትርክትን ለመገንባት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣና የኢትዮጵያ ሰላምንና አንድነትን ማጽናት እንደሚገባው አሳስበዋል።

ወጣቱ ግንቦት ወር የሚካሄደውን ጠቅላላ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ ምርጫ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶን በመምረጥ ሀገርን እንዲያስቀጥሉና እንዲያፀኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወጣቱ ንቁ ተሳታፊ በመሆኑ ብልፅግናን እንዲመርጡና የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶችን የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ኃይለማርያም በበኩላቸው፤ ወጣቶች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በታቀደው መሠረት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸው ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

‎ሀገር የምትገነባውና ህልውናዋ የሚጸናው በወጣት ኃይል ተሳትፎ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ እታገኝ፤ ወጣቶች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ ብቻ ሳይሆን ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ዘጋቢ፡ በቀሌች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን