ካይ ሀቨርትዝ ከጉዳቱ በቶሎ የማገገም ተስፋ አለው
አርሰናል በሳምንቱ መጨረሻ ከኒውካስል ጋር በነበረው ጨዋታ የጡንቻ ጉዳት ያስተናገደው ካይ ሀቨርትዝ፣ ለዋንጫ በሚደረገው ወሳኝ የውድድር ማጠናቀቂያ ላይ ለቡድኑ ግልጋሎት ይሰጣል የሚል ተስፋ አለው።
ይህ የ 26 ዓመቱ ጀርመናዊ አጥቂ፣ ቡድኑ በኤዲ ሀው ስብስብ ላይ ድል ባስመዘገበበት የቅዳሜው ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ በደረሰበት የጭን እግር ህመም ምክንያት ሜዳውን ለቆ ለመውጣት ተገዷል።
ክለቡ ተጫዋቹ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ግልጽ የሆነ የጊዜ ገደብ ባያስቀምጥም፣ አርሰናል ከ 2004 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለማንሳት በሚያደርገው ጥረት በሊጉ ቀሪ አራት ጨዋታዎች ላይ ሀቨርትዝ ይሳተፋል ተብሎ ይጠበቃል።
የሚኬል አርቴታ ስብስብ በሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይም የሚገኝ ሲሆን፣ በነገው እለት ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል።
ሀቨርትዝ በዚህ የውድድር ዘመን በጉልበት ጉዳት ምክንያት ለስድስት ወራት ያህል ከሜዳ ርቆ የነበረ ሲሆን፣ ከጥር ወር ጀምሮ ወደ ጨዋታ ከተመለሰ በኋላ ባደረጋቸው 19 ጨዋታዎች 5 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የማንቸስተር ሲቲ ጥያቄ ውድቅ ተደረገ
“በአሞሪም ጊዜ ሽንፈት ይከተለን ነበር፤ አሁን ግን ተለውጠናል!” – ሀሪ ማጓየር
የፕሪሚየር ሊጉ የሳምንቱ መሳጭ ፍልሚያዎች፡ አርሰናል መሪነቱን ለማስመለስ፣ ሊቨርፑል ለሦስተኛ ተከታታይ ድል!