ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
በ34ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን 1ለ0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍቅረየሱስ ተ/ብርሀን በመጀመሪያው አጋማሽ የሲዳማ ቡናን የማሸነፊያ ጎል አስገኝቷል።
ሲዳማ ቡና በዚህ ዓመት 17ኛ የሊግ ድሉን ሲያሳካ አዳማ ከተማ በአንፃሩ 11ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
ሲዳማ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 61 በማድረስ ከተከታዩ መቻል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 8 አስፍቷል።
አዳማ ከተማ በበኩሉ 39 ነጥቦችን ይዞ በወራጅ ቀጠናው አፋፍ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሊቨርፑል አሰልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናበተ
የጋብሪኤል ጄሱስ የወደፊት ዕጣ ፈንታ
ማንቸስተር ዩናይትድ የአታላንታውን አማካይ ኤደርሰንን ለማስፈረም ተቃረበ