ካይ ሀቨርትዝ 3ኛው ተጫዋች ሆነ

ካይ ሀቨርትዝ 3ኛው ተጫዋች ሆነ

ጀርመናዊው የፊት መስመር ተጫዋች ካይ ሀቨርትዝ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ለሁለት የተለያዩ ክለቦች ጎል ያስቆጠረ 3ኛው ተጫዋች ሆኗል።

ካይ ሀቨርትዝ በሀንጋሪ ቡዳፔስት ከተማ በፑሽካሽ አሬና ስታዲየም እየታከሄደ በሚገኘው የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ፒኤስጂ ላይ ጎል አስቆጥሮ አርሰናል መሪ ማድረግ ችሏል።

ይህንን ተከትሎ ካይ ሀቨርትዝ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ(ማንቸስተር ዩናይትድ፣ሪያል ማድሪድ) እና ከማሪዮ ማንዙኪች(ባየርን ሙኒክ፣ዩቨንቱስ) በመቀጠል በሻምፒዮንስ ሊጉ ፍፃሜ ጨዋታ ጎል ያስቆጠረ 3ኛው ተጫዋች ሆኗል።

ካይ ሀቨርትዝ ከዚህ ቀደም የቼልሲ ተጫዋች በነበረበት ወቅት ማንቸስተር ሲቲ ላይ ጎል አስቆጥሮ ሰማያዊዮቹን የሻምፒዮንስ ሊግ ባለድል ማድረጉ ይታወሳል።

ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ