ፓትሪክ ዶርጉ ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ ነው
የማንቸስተር ዩናይትዱ የመስመር ተመላላሽ ፓትሪክ በጉዳት ምክንያት ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተገልጿል።
ፓትሪክ ዶርጉ ማንቸስተር ዩናይትድ አርሰናልን 3ለ2 በረታበት እና ተጫዋቹ ጎል ባስቆጠረበት ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወሳል።
በጉዳቱ ምክንያት ዴንማርካዊው ተጫዋች ቢያንስ ለሁለት ወራት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።
የፓትሪክ ዶርጉ መጎዳት ከአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ስንብት ወዲህ አስደናቂ ክህሎቱን በማሳየት ላይ ለሚገኘው ተጫዋች እና ለክለቡ ጥሩ ዜና አይደለም።
የ22 ዓመት ፓትሪክ ዶርጉ ዩናይትድ በፕሪሚዬር ሊጉ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች መሪውን አርሰናልን እና ማንቸስተር ሲቲን ሲያሸንፍ ጎል ማስቆጠሩ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ቼልሲ፣አስቶንቪላ እና ፎረስት ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
ፌስቲቫሉ ከወድድርም ባለፈ የአብሮነታችንን ዕሴት ያጎለበተ ነበር ሲሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የታዳጊዎች ምዘናና የባህል ስፖርት ውድድር ፌስቲቫል ተሳታፊዎች ተናገሩ
በክብር እንግድነት ኢትዮጵያ የደረሰው ባካሪ ሳኛ