ፓትሪክ ዶርጉ ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ ነው

ፓትሪክ ዶርጉ ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ ነው

የማንቸስተር ዩናይትዱ የመስመር ተመላላሽ ፓትሪክ በጉዳት ምክንያት ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተገልጿል።

ፓትሪክ ዶርጉ ማንቸስተር ዩናይትድ አርሰናልን 3ለ2 በረታበት እና ተጫዋቹ ጎል ባስቆጠረበት ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወሳል።

በጉዳቱ ምክንያት ዴንማርካዊው ተጫዋች ቢያንስ ለሁለት ወራት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።

የፓትሪክ ዶርጉ መጎዳት ከአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ስንብት ወዲህ አስደናቂ ክህሎቱን በማሳየት ላይ ለሚገኘው ተጫዋች እና ለክለቡ ጥሩ ዜና አይደለም።

የ22 ዓመት ፓትሪክ ዶርጉ ዩናይትድ በፕሪሚዬር ሊጉ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች መሪውን አርሰናልን እና ማንቸስተር ሲቲን ሲያሸንፍ ጎል ማስቆጠሩ ይታወሳል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ