ፓትሪክ ዶርጉ ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ ነው
የማንቸስተር ዩናይትዱ የመስመር ተመላላሽ ፓትሪክ በጉዳት ምክንያት ለ10 ሳምንታት ያኽል ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተገልጿል።
ፓትሪክ ዶርጉ ማንቸስተር ዩናይትድ አርሰናልን 3ለ2 በረታበት እና ተጫዋቹ ጎል ባስቆጠረበት ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወሳል።
በጉዳቱ ምክንያት ዴንማርካዊው ተጫዋች ቢያንስ ለሁለት ወራት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።
የፓትሪክ ዶርጉ መጎዳት ከአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ስንብት ወዲህ አስደናቂ ክህሎቱን በማሳየት ላይ ለሚገኘው ተጫዋች እና ለክለቡ ጥሩ ዜና አይደለም።
የ22 ዓመት ፓትሪክ ዶርጉ ዩናይትድ በፕሪሚዬር ሊጉ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች መሪውን አርሰናልን እና ማንቸስተር ሲቲን ሲያሸንፍ ጎል ማስቆጠሩ ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ከሚያዝያ 22 ጀምሮ በጂንካ ከተማ ለሚስተናገደው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ግምገማ መካሄዱን የክልሉ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከስታወቀ
የማንቸስተር ሲቲ ጥያቄ ውድቅ ተደረገ
ካይ ሀቨርትዝ ከጉዳቱ በቶሎ የማገገም ተስፋ አለው