ማክስ ዳውማን ከአርሰናል ጋር የስኮላርሺፕ ውል ተፈራረመ
እንግሊዛዊው ታዳጊ ተጫዋች ማክስ ዳውማን ከአርሰናል ጋር የስኮላርሺፕ ውል ተፈራርሟል።
የመስመር ተጫዋቹ በቅርቡ 16 ዓመት ስለሞላው የስኮላርሺፕ ኮንትራት የተፈራረመ ሲሆን በቀጣይ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ 17 ዓመት ሲሆነው የመጀመሪያውን የፕሮፌሽናል ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
በ15 ዓመቱ ለመድፈኞቹ ዋናው ቡድን ተሰልፎ መጫወት የቻለው ዳውማን ከቡድን አጋሩ ኤታን ንዋኔሪ በመቀጠል በፕሪሚዬር ሊጉ መጫወት የቻለ ሁለተኛው በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ነው።
አሁን ላይ በጉዳት ምክንያት ከጨዋታ ርቆ የሚገኘው ማክስ ዳውማን ለአርሰናል እስካሁን በቨ5 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ካይ ሀቨርትዝ 3ኛው ተጫዋች ሆነ
ኢትዮጵያ ቡሩንዲን በደርሶ መልስ አሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈች
ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ