ማክስ ዳውማን ከአርሰናል ጋር የስኮላርሺፕ ውል ተፈራረመ
እንግሊዛዊው ታዳጊ ተጫዋች ማክስ ዳውማን ከአርሰናል ጋር የስኮላርሺፕ ውል ተፈራርሟል።
የመስመር ተጫዋቹ በቅርቡ 16 ዓመት ስለሞላው የስኮላርሺፕ ኮንትራት የተፈራረመ ሲሆን በቀጣይ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ 17 ዓመት ሲሆነው የመጀመሪያውን የፕሮፌሽናል ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
በ15 ዓመቱ ለመድፈኞቹ ዋናው ቡድን ተሰልፎ መጫወት የቻለው ዳውማን ከቡድን አጋሩ ኤታን ንዋኔሪ በመቀጠል በፕሪሚዬር ሊጉ መጫወት የቻለ ሁለተኛው በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ነው።
አሁን ላይ በጉዳት ምክንያት ከጨዋታ ርቆ የሚገኘው ማክስ ዳውማን ለአርሰናል እስካሁን በቨ5 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሲዳማ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
ማንቸስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4ለ0 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፈ
አሌክሳንደር አይሳክ ወደ ልምምድ ሊመለስ ነው