ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
ሀዋሳ፡ ጥር 14/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ 16ኛ ሳምንት መጨረሻ መርሐግብር ግብር ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።
ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ከሁለት ተከታታይ የአቻ ውጤት በኋላ ሲዳማ ቡና ወደ አሸናፊነት ተመልሷል።
በአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ ለሚመራው ሲዳማ ቡና የማሸነፊያ ጎሎችን ብለስ ናጎ ፣ ፍራኦል መንግስቱ እና ዮሴፍ ዮሐንስ አስገኝተዋል።
9ኛ የሊግ ድሉን ያሳካው ሲዳማ ቡና ነጥቡን 33 በማድረስ ከተከታዩ ሀዋሳ ከተማ በአምስት ነጥብ ርቆ ሊጉን እየመራ ይገኛል።
7ኛ የሊግ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና በአንፃሩ በ19 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ