ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ

ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ

ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ከስምምነት ላይ መድረሱ ተገልጿል።

ማንቸስተር ሲቲ እንግሊዛዊውን የመሀል ተከላካይ ለማስፈረም ከፓላስ ጋር በመርህ ደረጃ መስማማቱን ቢቢሲ አስነብቧል።

ማንቸስተር ሲቲ ከጉሂ ጋር በግል ጉዳይ ከስምምነት ላይ ባይደርስም ተጫዋቹን ለማሳመን ላይቸገር ይችላል ተብሏል።

የክርስቲያል ፓላሱ አሰልጣኝ ኦሊቨር ግላስነር ተጫዋቹ ማንቸስተር ሲቲን ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱን ተናግረዋል።

ሲትዝኖቹ የ25 ዓመቱን ተጫዋች ለማስፈረም 20 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ማቅረባቸው ተዘግቧል።

ዘጋቢ ፡ በሙሉቀን ባሳ