የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ
ከአምስቱ የእስልምና መሰረቶች አንዱ ሀጅ ነው ያሉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸህ አብዱሽኩር፤ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቅም በፈቀዱለት የእስልምና ላይ ሁሉ ግዴታ የተደረገ የአምልኮ ስርዓት መሆኑንም ገልፀዋል።
በዚህም በየአመቱ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሙስሊሞች የሀጅ ተግባር እንደሚፈፅሙ የተናገሩት ሀላፊው፤ ዘንድሮ የተፈቀደልንን 43 ሺህ ሙስሊሞችን የማሳተፍ እድል ለመጠቀም ምዝገባ እያካሄድን እንገናኛለን ነው ያሉት።
ይሁንና በዚህ አመት የምዝገባው ጊዜ ቀድሞ በመጀመሩ ሙስሊምች በወቅቱ መጥተው እየተመዘገቡ አይደለም ያሉት ሸህ አብዱ ሽኩር፤ የምዝገባ ጊዜው ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሚጠናቀቅ በእነዚህ ጊዜያት መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ሰብስቤ አደም

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ