የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ
ከአምስቱ የእስልምና መሰረቶች አንዱ ሀጅ ነው ያሉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸህ አብዱሽኩር፤ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቅም በፈቀዱለት የእስልምና ላይ ሁሉ ግዴታ የተደረገ የአምልኮ ስርዓት መሆኑንም ገልፀዋል።
በዚህም በየአመቱ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሙስሊሞች የሀጅ ተግባር እንደሚፈፅሙ የተናገሩት ሀላፊው፤ ዘንድሮ የተፈቀደልንን 43 ሺህ ሙስሊሞችን የማሳተፍ እድል ለመጠቀም ምዝገባ እያካሄድን እንገናኛለን ነው ያሉት።
ይሁንና በዚህ አመት የምዝገባው ጊዜ ቀድሞ በመጀመሩ ሙስሊምች በወቅቱ መጥተው እየተመዘገቡ አይደለም ያሉት ሸህ አብዱ ሽኩር፤ የምዝገባ ጊዜው ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሚጠናቀቅ በእነዚህ ጊዜያት መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ሰብስቤ አደም

More Stories
በስራ ቦታቸው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል መቋቋሙ ስራቸውን በአግባቡ ለማከናወን እንዳስቻላቸው የማእከሉ ተጠቃሚ እናቶች ገለፁ
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ
በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል