የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ
ከአምስቱ የእስልምና መሰረቶች አንዱ ሀጅ ነው ያሉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸህ አብዱሽኩር፤ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቅም በፈቀዱለት የእስልምና ላይ ሁሉ ግዴታ የተደረገ የአምልኮ ስርዓት መሆኑንም ገልፀዋል።
በዚህም በየአመቱ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሙስሊሞች የሀጅ ተግባር እንደሚፈፅሙ የተናገሩት ሀላፊው፤ ዘንድሮ የተፈቀደልንን 43 ሺህ ሙስሊሞችን የማሳተፍ እድል ለመጠቀም ምዝገባ እያካሄድን እንገናኛለን ነው ያሉት።
ይሁንና በዚህ አመት የምዝገባው ጊዜ ቀድሞ በመጀመሩ ሙስሊምች በወቅቱ መጥተው እየተመዘገቡ አይደለም ያሉት ሸህ አብዱ ሽኩር፤ የምዝገባ ጊዜው ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሚጠናቀቅ በእነዚህ ጊዜያት መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ሰብስቤ አደም

More Stories
3ኛው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክለቦች ሻምፒዮና የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ