የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ
ከአምስቱ የእስልምና መሰረቶች አንዱ ሀጅ ነው ያሉት የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸህ አብዱሽኩር፤ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቅም በፈቀዱለት የእስልምና ላይ ሁሉ ግዴታ የተደረገ የአምልኮ ስርዓት መሆኑንም ገልፀዋል።
በዚህም በየአመቱ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሙስሊሞች የሀጅ ተግባር እንደሚፈፅሙ የተናገሩት ሀላፊው፤ ዘንድሮ የተፈቀደልንን 43 ሺህ ሙስሊሞችን የማሳተፍ እድል ለመጠቀም ምዝገባ እያካሄድን እንገናኛለን ነው ያሉት።
ይሁንና በዚህ አመት የምዝገባው ጊዜ ቀድሞ በመጀመሩ ሙስሊምች በወቅቱ መጥተው እየተመዘገቡ አይደለም ያሉት ሸህ አብዱ ሽኩር፤ የምዝገባ ጊዜው ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሚጠናቀቅ በእነዚህ ጊዜያት መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ሰብስቤ አደም

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ