አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ

አርሰናል በአስቶንቪላ ተሸነፈ

በ15ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ከሜዳው ውጪ ከአስቶንቪላ ጋር የተጫወተው የሊጉ መሪ አርሰናል ሽንፈትን አስተናግዷል።

እጅግ እልህ አስጨራሽ የነበረው እና 30 ሙከራዎች የተደረጉበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአስቶንቫላ 2ለ1 አሸናፊነት  ተጠናቋል።

ለአስቶንቪላ ወሳኝ የማሸነፊያ ጎሎችን ማቲ ካሽ እና ኢሚሊያኖ ቡንዲያ አስገኝተዋል።

አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችውን ጎል ደግሞ ሊያንድሮ ትሮሳርድ አስቆጥሯል።

ሊያንድሮ ትሮሳርድ በፕሪሚዬር ሊጉ 50ኛ ጎሉን አስቆጥሯል።

ፖላንዳዊው የቀኝ መስመር ተከላካይ ማቲ ካሽ በዚህ ዓመት 3ኛ የሊግ ጎሉን አስቆጥሯል።

አርሰናል በሁሉም ውድድሮች ከ18 ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈትን አስተናግዷል።

አስቶንቪላ በሊጉ 5ኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

አስቶንቪላ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 30 በማድረስ ከመሪው አርሰናል በ3 ነጥብ አንሶ 2ኛ ደረጃን ይዟል።

በሊጉ 2ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርሰናል በ33 ነጥብ የደረጃ ሰንጠረዡን እየመራ ይገኛል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ