አሽራፍ ሀኪሚ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
ሞሮኳዊው የመስመር ተከላካይ አሽራፍ ሀኪሚ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።
አሽራፍ ሀኪሚ የመጨረሻ እጩ ሆነው የቀረቡትን ሞሐመድ ሳላን እና ቪክቶር ኦሲምሄን በመብለጥ ነው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ያሸነፈው።
የፒኤስጂው ተጫዋች በ2024/25 የውድድር ዓመት ያሳየው ድንቅ ብቃት ለዚህ ሽልማት አብቅቶታል።
የ27 ዓመቱ ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ውስጥ ከፈረንሳዩ ክለብ ጋር የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፣ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ፣ የፍሬንች ሊግ ኣ እና የኮፕ ዴ ፍራንስ ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል።
ከዚህም ባሻገር የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ወደ 2026 የዓለም ዋንጫ ስታልፍ ከፍተኛ ድርሻ ተወጥቷል።
አሽራፍ ሀኪሚ ሙስጠፋ ሀጂ እንደ አውሮፓውያኑ በ1998 የዓመቱ ምርጥ ሽልማትን ካሸነፈ በኋላ ይህንን ሽልማት ያሸነፈ የመጀመሪያው ሞሮኳዊ ተጫዋች መሆን ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የዘንድሮ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በሀገራችን የዲሞክራሲያዊ ስርዓት እያደገ መምጣቱን አሳይቷል – የዩኒቨርሲቲ ምሁራን
ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
በክልሉ የተጀመረውን የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከግጭት የጸዳ አካባቢ ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላም እና ፀጥታ ቢሮ አሳሰበ