አሽራፍ ሀኪሚ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
ሞሮኳዊው የመስመር ተከላካይ አሽራፍ ሀኪሚ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።
አሽራፍ ሀኪሚ የመጨረሻ እጩ ሆነው የቀረቡትን ሞሐመድ ሳላን እና ቪክቶር ኦሲምሄን በመብለጥ ነው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ያሸነፈው።
የፒኤስጂው ተጫዋች በ2024/25 የውድድር ዓመት ያሳየው ድንቅ ብቃት ለዚህ ሽልማት አብቅቶታል።
የ27 ዓመቱ ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ውስጥ ከፈረንሳዩ ክለብ ጋር የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፣ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ፣ የፍሬንች ሊግ ኣ እና የኮፕ ዴ ፍራንስ ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል።
ከዚህም ባሻገር የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ወደ 2026 የዓለም ዋንጫ ስታልፍ ከፍተኛ ድርሻ ተወጥቷል።
አሽራፍ ሀኪሚ ሙስጠፋ ሀጂ እንደ አውሮፓውያኑ በ1998 የዓመቱ ምርጥ ሽልማትን ካሸነፈ በኋላ ይህንን ሽልማት ያሸነፈ የመጀመሪያው ሞሮኳዊ ተጫዋች መሆን ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽንስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
አካል ጉዳተኝነት ውጤታማ ከመሆን ያልገደባቸው አቶ ሀብታሙ ለማ
የፈተና አስተዳደር ሥርዓትን በማዘመን ኩረጃን በማስቀረት የተሻሉ ተማሪዎችን ማፍራት እየተቻለ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ