ጋብርኤል ማጋሌሽ የጡንቻ ጉዳት እንዳጋጠመው ተገለፀ
የአርሰናል የመሀል ስፍራ ተከላካይ በቀኝ እግሩ ጡንቻ ላይ ጉዳት እንዳጋጠመው ተገልጿል።
ጋብርኤል ማጋሌሽ ብራዚል ከሴኔጋል ጋር ባካሄደችው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል።
የመድፈኞቹ የኋላ ደጀን የጡንቻ ጉዳት እንዳጋጠመው መረጋገጡን ተከትሎ በፈረንሳይ ሊል ብራዚል ከቱኒዚያ ጋር ማክሰኞ ዕለት ከምታደርገው ሌላኛው የወዳጅነት ጨዋታ ውጪ ሆኗል።
ጋብርኤል ማጋሌሽ አርሰናል በቀጣይ ከቶትንሃም፣ ባየር ሙኒክ እና ቼልሲ ጋር በሚያከናውናቸው ወሳኝ ጨዋታዎች ላይሰለፍ እንደሚችል ተነግሯል።
የ27 ዓመቱ ተጫዋች አርሰናል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በፕሪሚየር ሊጉ በ11 ጨዋታዎች 5 ጎሎች ብቻ ተቆጥሮበት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አናት ላይ እንዲቀመጥ ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱ ባሻገር ሁለት ወሳኝ ጎሎችን ከመረብ አሳርፏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የጎዳና ሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል