ማንቸስተር ሲቲ የፊል ፎደን ውል ለማራዘም ስራ መጀመሩ ተገለፀ
የእንግሊዙ ክለብ ማንቸስተር ሲቲ የወሳኙን ተጫዋች ፊል ፎደንን ኮንትራት ለማራዘም ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
ከክለቡ አካዳሚ የተገኘው ፎደን በአሁኑ ሰዓት ከሲቲዝኖቹ ጋር ያለው ውል ከሁለት ዓመት በኋላ ይጠናቀቃል።
በዚህ ዓመት የቀደመ ብቃቱን መልሶ ያገኘ በሚመስለው የ25 ተጫዋች ብቃት ደስተኛ የሆኑት የክለቡ አመራሮች ውሉን ለማራዘም እየሰሩ መሆኑ ተዘግቧል።
ከመጋቢት ወር በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ የቀረበለት ፎደን በክለቡ ለመቆየት የሚያደርገው ድርድር በስምምነት እንደሚቋጭ ተስፋ ተጥሎበታል።
ድርድሩ በስምምነት የሚቋጭ ከሆነ በኤቲሐድ እስከ 2030 ድረስ የሚያቆየውን የ5 ዓመት ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ
ጆሿ ዚርኪዜ በሮማ ይፈለጋል