በቡርጂ ዞን የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ መርሃግብር ተካሂዷል።
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት በቡርጂ ዞን የማህበራዊ ክላስተር ኃላፊ አቶ ማሙሽ ማነ፤ የበጎ ፈቃድ ሥራ መንግስት ሊያወጣ የነበረውን ወጪ ማዳን ብቻ ሳይሆን የአእምሮ እርካታ መሠረት አድርጎ የሚሠራ ተግባር ነው ብለዋል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈፃፀምን አስመልክቶ የቡርጂ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት ዩኒት አስተባባሪ አቶ በየነ አሊ፤ የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በ15 ዘርፎች 25 ሺህ 9 መቶ 83 ወጣቶች መሳተፋቸውንና 41 ሺህ 7 መቶ 50 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ በከተማ ደረጃ መንግስት ሊያወጣ የነበረውን 23 ሚሊዮን 4 መቶ 87 ሺህ 8 መቶ 9 ብር ማዳን መቻሉን አብራርተዋል።
በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት ውይይት የተደረገ ሲሆን በክረምቱ ታቅደው የተከናወኑ ተግባራት መልካም ቢሆኑም በሎጂስቲክ እጥረት ምክንያት አገልግሎት ያላገኙ ቀበሌዎች በቀጣይ ለበጋው የበጎ ፈቃድ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ሀሳብ ቀርቧል።
ከመድረኩ ተሳታፊዎችም በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰጣቸውን ተግባር በአግባቡ ለማከናወን አስቸጋሪ ሁኔታዎች እንደነበሩ አንስተው፤ ህብረተሰቡም ሆነ ባለድርሻ አካላት የተግባሩን አስፈላጊነት በመገንዘብ ትኩረት እንዲሰጡበት ጠይቀዋል።
በበጎ ፈቃድ ተግባር ወቅት የተሻለ አፈፃፀም ያሳዩ ግለሰቦች እና ተቋማት ሽልማት እና እውቅና አግኝተዋል።
በመርሃግብሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ